መሠረታዊ ኦርቶዶክስ አስተምህሮ

 

ፍቅር ቊስል ነው

ጸሐፊ: Fr Haralambos Libyos Papadopoulos

በግሪክhttp://plibyos.blogspot.com/2018/04/blog-post_11.html

 በእንግሊዘኛhttp://www.oodegr.com/english/koinwnia/koinwnika/Love_is_a_wound.htm

 

 

እውነቱ ይህ ነው ፍቅር የሚለካው በልባችን ላይ በተወው ቊስል ልክ ነው።

እጅግ የምንወዳቸው ሰዎች አሳምመውን ይሆናል።

እኛም እጅግ የሚወዱንን ሰዎች አሳምመን ይሆናል።

ምክንያቱም ፍቅር የሚታየው በታገስነው ቊስል ውስጥ ነው

ፍቅር የሚታወቀው የተለዋወጥናቸውን ቃላት ሳይሆን በምንታገሠው ቊስል በተሰማን የውስጥ ሕመም በከፈልነውን መሥዋዕትነትና በተካፈልነውን ብርሃን ነው።

ከትንሣኤው በኋላ በሐዋርያቱ ፊት የተገለጠው ክርስቶስ እርሱ የሚወዱት ጌታ እንደሆነ ለማስረዳት ያሳያቸው የትንሣኤው ድል ማብሠሪያ መለከት አይደለም የፍቅሩ ማስረጃ ቊስሉ ነበር።

"ወደ እኔ ቊስሌን ዳስሱ እጃችሁንም ስለ እናንተ ፍቀር በቆሰልሁት ቊስል አስገቡ" ነበር ያላቸው።

አታስታውሱኝም? አላወቃችሁኝም? እስከ ሞት ድረስ የወደድኳችሁ እኔ ነኝ። ለፍቅሬ ማረስጃ እንዲሆናችሁ ደግሞ ቊስሌን ተመልከቱ! ነው ያላቸው።

ፍቅር ቊስል ነው።

በእግዚአብሔር መንግሥት ክብርና ምስጋና የምናገኘውም በምድር ሳለን በነበሩ ስኬቶቻችንና ባስገኘናቸው ውጤቶቻችን ሳይሆን በታገሥናቸው መከራዎችና በተሰቃየንባቸው ሕመሞች ልክ ነው።

ለዚህም ነው በአበው መጽሐፍ ቅዱስ ፓኢሲኦስ ለረጅም ዓመት በሰውነትዋ ላይ ቆስሎ የምትሰቃይን ሴት ሊጠይቁ ሲሔዱ

"እዩት ቊስሌን አጎንብሰው ቢያዩት አጥንቴ ይታይዎታል" አለቻቸው።

እርሳቸውም ጎንበስ ብለው "ብዙ ዓመት በታገስሽው በቊስልሽ ውስጥ የሚታየኝ አጥንት ሳይሆን ገነት ነው" አሏት።

 

ተርጓሚ: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ አዲስ አበባ